(7 8 )

Amharic Language, Literature And Folklore Project Topics

Get the Complete Project Materials Now! »

የዚህ ጥናት ዋና አላማ በሰበታ መርሐ እውራን ልዩ ትምህርት ቤት የአማርኛ ቋንቋrnየአንብቦ መረዳት ትምህርት ትግበራ ምን እንደሚመስልና የአይነስውር ተማሪዎችንrnልዩ ፍላጎትና ሁኔታ ከግምት ያስገባ መሆን አለመሆኑን መፈተሽ ነው፡፡ ከዚህrnአጠቃላይ ግብ ለመድረስ የአይነታዊ ምርምር ንድፍ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ የጥናቱrnተሳታፊዎችም የሰበታ መርሐ እውራን ልዩ ትምህርት ቤት የ2010 ዓ.ም የ7ኛ እናrn8ኛ ክፍል አይነስውር ተማሪዎች እንዲሁም የአማርኛ ቋንቋ የሚያስተምሩrnመምህራን ናቸው፡፡ የጥናቱ ተሳታፊዎች በወሳኝ የናሙና አመራረጥ፣ በጠቅላይrnየናሙና አመራረጥ፣ በኮታ የናሙና አመራረጥ እንዲሁም በብድግ ብድግ የናሙናrnአመራረጥ ስሌት ተመርጠዋል፡፡ ለመረጃ መሰብሰቢያ የተመረጡ መሳሪያዎች ደግሞrnየክፍል ውስጥ ምልከታ፣ የጽሁፍ መጠይቅ፣ ቃለመጠይቅና የተተኳሪ ቡድን ውይይትrnናቸው፡፡ የጥናቱ ግኝትም አጠቃላይ የመማሪያ ክፍል ሁኔታው የአይነስውርrnተማሪዎችን የንባብ ትምህርት ሂደት የሚደግፍ፣ አግባብነት ያለው፣ ተስማሚና ምቹrnእንደሆነ ታይቷል፡፡ የቅድመ ንባብ፣ የንባብ ጊዜ እና የድህረ ንባብ ትምህርትrnጊዜዎች በተለያዩ ተግባራት ታጅበው የሚከናወኑና በአብዛኛው በጥሩ ሁኔታ ላይrnየሚገኝ ቢሆንም፤ የአይነስውር ተማሪዎችን ልዩ ፍላጎት ከግምት ባስገባ መልኩrnአስማምቶና አጣጥሞ ማቅረብ ላይ፣ አይነስውር ተማሪዎቹን ማእከል ያደረገ በቂrnየንባብ ጊዜ ከመመደብ/ከመስጠት አንጻር እንዲሁም የአይነስውር ተማሪዎችን የንባብrnትምህርት ለማጎልበት የሚረዱ ስልቶችንና ብልሀቶችን ከማስተዋወቅናrnእንዲጠቀሙባቸው ከማበረታታትና ከማገዝ አኳያ ክፍተቶች ታይተዋል፡፡ እነዚህንrnክፍተቶች ለመድፈንና ለተሻለ የአይነስውራን የንባብ ትምህርት ሂደት ይረዳሉrnየተባሉ ሀሳቦችም ተሰንዝረዋል፡፡ ከነዚህም ውስጥ የአንብቦ መረዳት ትምህርትrnስልቶችና ብልሀቶችን የሚያስተዋውቅና ከዘመኑ ጋር የሚሄድ ስልጠና ለአማርኛrnቋንቋ መምህራን ማመቻቸት፣ የንባቡን ርእስ እና ይዘት ከተማሪዎች ልዩ ፍላጎትናrnሁኔታ ጋር አጣጥሞና አስማምቶ ማቅረብ እንዲሁም የአይነስውር ተማሪዎችንrnአንብቦ መረዳት የሚያጎለብቱ እንደ ተዳሳሽ ቁስ፣ የድምጽ ግብአትና እውን ቁሶችንrnከንባብ ትምህርቱ ጋር በማዛመድ ተግባራዊ ማድረግ የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው፡፡

Get Full Work

Report copyright infringement or plagiarism

Be the First to Share On Social



1GB data
1GB data

RELATED TOPICS

1GB data
1GB data
(7  8  )

258