( )

Amharic Language, Literature And Folklore Project Topics

Get the Complete Project Materials Now! »

የዚህ ጥናት ዋና አላማ በአማርኛ ቋንቋ መምህራን የተግባቦት ክህሎት አጠቃቀምና በክፍል ውስጥrnመስተጋብር አተገባበሩ መካከል ተዛምዶ መኖሩን መመርመር ነው፡፡ በዚህ መሰረት ጥናቱ የተጠኝrnመምህራኑን የተግባቦት ክህሎት አጠቃቀምና የክፍል ውስጥ መስተጋብር አተገባበሩን እንዴትነትrnከተመለከተ በኋላ በመካከላቸው ተዛምዶ መኖሩን መርምሯል፡፡ ምርምሩ የተከናወነው በድኅረrnአወንታውያን የምርምር ቀመረ እሳቤና በመሰረተ ግንባታውያን የመማር ንድፈ ሀሳቦች ዝንቅrnማሕቀፍነት ነው፡፡ መነጸሪያው እስካሁን ድረስ የተሰነዘሩ ቋንቋን የመማር ንድፈ ሀሳቦች ዝንቅ ሲሆንrnየጥናቱ ሞዴል ለጥናቱ እንዲመች ተደርጎ የተቀናበረ ተግባ-ግብይታዊ የመማር ማስተማር ሂደትrnማሕቀፍ ነው፡፡ ለጥናቱ ጥምር የምርምር ንድፍና ተዛምዷዊ የምርምር ስልት በጥቅም ላይ ውለዋል፡፡rnመረጃዎች በይሆንታዊና ኢይሆንታዊ የንሞና ዘዴዎች ከተመረጡ ተጠኝዎች በአጭር ጊዜ ምልከታ፣rnበተመራማሪ እለታዊ ማስታወሻና በሰነድ ምርመራ የተሰበሰቡ ሲሆን የተተነተኑት በይዘት ትንታኔናrnበሰነድ ትንታኔ ነው፡፡ በዚህ መሰረት በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሂደት በመምህራኑ የተግባቦት ክህሎትrnአጠቃቀምና በክፍል ውስጥ መስተጋብር አተገባበሩ መካከል ጠንካራ አወንታዊ ተዛምዶ መኖሩን ለማወቅrnተችሏል፡፡ የመምህራኑ የተግባቦት ክህሎት አጠቃቀምም ሆነ የክፍል ውስጥ መስተጋብሩ ከሚጠበቀውrnአንጻር ደካማ ናቸው፡፡ በተግባቦት ክህሎት አጠቃቀምም ሆነ በክፍል ውስጥ መስተጋብር አተገባበርrnረገድ የትምህርት ደረጃቸው ዲግሪ የሆነ መምህራን የትምህርት ደረጃቸው ዲፕሎማ ከሆኑ መምህራንrnተሽሎ የተገኘ ቢሆንም በሁለቱም የትምህርት ደረጃ ያሉ መምህራን የተግባቦት ክህሎት አጠቃቀምናrnየክፍል ውስጥ መስተጋብር አተገባበር ከሚጠበቀው አንጻር ደካማ ነው፡፡

Get Full Work

Report copyright infringement or plagiarism

Be the First to Share On Social



1GB data
1GB data

RELATED TOPICS

1GB data
1GB data
(          )

217